ፋሲል ከነማ አጥቂ አስፈርሟል !

ከዝህ ቀደም በኦሜድላ (ፌዴራል ፖሊስ) ፣ ነገሌ አርሲ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና አርባ ምንጭ ከተማ መጫወት የቻለው አጥቂው ታምራት ኢያሱ ፋሲል ከነማን ተቀላቅሏል።

ታምራት ኢያሱ በመጀመሪያ ዙር ለአርባ ምንጭ ከተማ 7 ግቦች በማስቆጠር የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪዎች መካከል አንዱ ነው።

ፋሲል ከነማ በመጀመሪያ ዙር ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 19 ጨዋታዎችን አድርጎ 33 ነጥቦችን በመሰብሰብ 4ኛ ደረጃ ላይ ይገኛ።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *