መቐለ 70 እንደርታ ሶስት ጨዋታዎችን በፎርፌ ተሸናፊ እንድሆን ቅጣት ተላለፈበት!

መቐለ 70 እንደርታ ሶስት ጨዋታዎች በፊርፌ ተሸናፊ እንድሁን ቅጣት ተላለፈ!

መቐለ 70 እንደርታ እግር ኳስ ክለብ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በነበረው 7ኛ ሳምንት ጨዋታ በ 2017 ውድድር ዘመን 30ኛ (የመጨረሻው ሳምንት) ጨዋታ በቀይ ካርድ ከሜዳ የተወገደውንና አራት ጨዋታ እንድታገድ የተወሰነበትን ሱለይማን ሃሚድ መታወቂያ ቁጥር EFF-18-77/ የተባለ ተጫዋች ያለፉትን 6 ጨዋታዎች አሰልፎ ስለማጫወቱና በዚህም የፎርፌ ውጤት ይገባኛል በማለት ከኢትዮጲያ ንግድ ባንክ ክስ ቀርቦበታል።

የውድድር ስነ-ስረዓት ኮሚቴ የቀረበውን ክስ መነሻ በማድረግ ባካሄደው ማጣራት ተጨዋቹ ለመቐለ 70 እንደርታ በ2ኛ ሳምንት ከመቻል ፣ በ3ኛ ሳምንት ድሬዳዋ ከተማ እና በ4ኛ ሳምንት ከሀዋሳ ከተማ በተደረጉ ጨዋታዎች ቅጣቱን ሳይጨርስ ተሰልፎ እንዳጫወተ አረጋግጧል።

ስለሆነም ክለቡ /መቐለ 70 እንደርታ/ ተገቢ ያልሆነ ተጨዋች አሰልፎ በማጫወቱ ለፈፀመው ጥፋት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 5 አንቀጽ 36 (ሐ) መሰረት ከ2ኛ እስከ 4ኛ ሳምንት ያሉትን 3 ጨዋታዎች ውጤት ተሰርዞ በፎርፌ ተሸናፊ እንዲሆን (ሶስቱንም ጨዋታዎች 0 ነጥብ እና 3 የግብ እዳ እንድመዘገብበትና እና ለተጋጣሚዎቹ መቻል ፣ ድሬዳዋ ከተማ እና ሀዋሳ ከተማ 3 ነጥብና 3 ነጥብ እንድመዘገብላቸው/ በተጨማሪም ብር 20ሺህ/ እንድከፍል እንዲሁም የቡድን መሪው 6 ወር እንድታገድ የውድድር ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።