የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባለፈው ሳምንት ለንባብ በበቃው ጋዜጣችን በቀን 23/2013 በቁጥር 655 The Big Interview በሚለው አምዳችን የብሔራዊ ፌዴሬሽኑ የቴክኒክ ኮሚቴ አባልና የአዲስ አበባ እግር ኳስ አሰልጣኞች ማህበር ዋና ፀሐፊ የሰጡትን ቃለ ምልልስ ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተሰማውን ቅሬታ በቀን 29/01/13 ዓ.ም በቁጥር 2/ኢ.እ.ፌ.አ.3/1806 በጽ/ቤት ኃላፊው በአቶ ባህሩ ጥላሁን ልመንህ ተፈርሞ በተፃፈ ደብዳቤ ገልፀውልናል፡፡
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለሌሎችም ምሣሌ በሚሆን መልኩ የፕሬስ ሕጉ የሚፈቅደውንና ሃሣብን በሃሣብ የመታገል የሰለጠነ መንገድ በጉዳዩ ዙሪያ የቀረበውን ቅሬታ በዝግጅት ክፍላችን አንዳችም የአርትኦት ስራ ሣይደረግበት እንዳለ ማቅረባችንን እየገለፅን ፌዴሬሽኑ ለመረጠው የሰለጠነ መንገድ ያለንን አድናቆት ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ ፌዴሬሽኑ ለዝግጅት ክፍላችን የላከው የቅሬታ ደብዳቤ ከዚህ በታች ቀርቧል፡፡
